Wednesday 10 April 2013

መግለጫ በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ አካል ነዉ!


Posted April 1  Ginbot7

Untitledg7hhh
የወያኔ መሪዎች እነ መለስ ዜናዊና ስብሐት ነጋ በ1967 ዓም ለትግል ደደቢት በረሀ እንዲገቡ ያነሳሳቸዉና ያሰባሰባቸዉ በአማራዉ ህዝብ ላይ ያላቸው ጥላቻና የበቀል ስሜት እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ በደልና እሮሮ አንገፍግፏቸዉ እንዳልሆነ በተለያዩ ግዜዎች ለህዝብ ይፋ የሆኑት የወያኔ መግለጫዎችና ለረጂም ግዜ ወያኔን የመሩት መለስ ዜናዊና ስብሐት ነጋ በየአደባባዩ ላይ ያደረጓቸዉ ንግግሮች በግልጽ ያሳያሉ። እነዚህ ከወጣትነት ግዜያቸዉ ጀምሮ በአማራ ህዝብ ላይ ጥርሳቸዉን የነከሱ የወያኔ መስራቾች በለስ ቀንቷቸዉ አዲስ አበባን ከተቆጣጠሩ በኋላም ቢሆን ለአማራ ህዝብ፤ ባህልና ታሪክ ያለቻዉ ጥላቻ ከተራ ጥላቻ አልፎ በተግባር አማራዉን ወደ ማጥቃት ዘመቻ አደገ እንጂ ለአንድም ቀን ቀንሶ አያውቅም።
የወያኔ አገዛዝ ኢትዮጵያ ውስጥ ያከበረዉ ወይም የኤኮኖሚና የፖለቲካ ጥቅሙን ያስጠበቀለት ብሔረሰብ ባይኖርም በግለሰብ ደረጃም ሆነ በቡድን የወያኔ ዘረኞች የአማራን ህዝብ ከተቀሩት ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቹና እህቶቹ ነጥለዉ ለማጥቃትና የስነ ልቦና ዘይቤውን ለመስበር ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል። በአጠቃላይ የወያኔ ዘረኛ ባለስልጣኖች አማራውን በተከታታይ ሲዘልፉ ቆይተዋል፤አዋርደው አስረዋል፤ ከአገር እንዲሰደድ አድረገዋል፤ አፈናቅለዋል ገድለዋል። ለምሳሌ ወያኔ ስልጣን በያዘባቸዉ በመጀመሪያዎቹ አምስት አመታት ዉስጥ ብቻ አሶሳ፤ በደኖና አርባጉጉ ውስጥ አማራ በመሆናቸዉ ብቻ ህጻናት፤ሴቶችና አረጋዉያን በግፍ ተገድለዋል። ባለፈዉ አመት በደቡብ ክልል ጉራ ፈርዳ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ ለረጂም አመታት ከአካባቢዉ ኢትዮጵያዊ ወገናቸው ጋር ተግባብተዉ ይኖሩ የነበሩ የአማራ ተወላጆች አማራ በመሆናቸዉ ብቻ ለአመታት ያፈሩትን ንብረት ይዞ የመሄጃ ግዜ እንኳን ሳይሰጣቸዉ አከባቢዉን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለቅቀዉ እንዲወጡና እንዲፈናቀሉ ተደርጓል። የወያኔ ባለስልጣኖችና በየአካባቢዉ የኮለኮሏቸዉ ምስለኔዎች አካባቢዉን በግድ እንዲለቅ የተደረገ ህግ አክባሪ ዜጋ የለም፤ የተባረሩት ህግ የጣሱ ግለሰቦች ብቻ ናቸው፣
በማለት አሳፋሪ ድርጊታቸዉን ለመደበቅ ሲሞክሩ ታይተዋል። ሆኖም ከጉራ ፈርዳና ከአካባቢዉ ተፈናቅለዉ ወደ መጣችሁበት አካባቢ ተመለሱ ተብለው በየሜዳው ያለምግብ፣ ውኃና፤መጠለያ የተበተኑ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጆች ለወገኖቻቸውና ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ የድረሱልን ጩኸት ሲያሰሙ መሰንበታቸዉ የቅርብ ግዜ ትዝታ ነዉ። ወያኔ በዚህ በያዝነዉ አመት ከመጋቢት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በአማራዉ ህዝብ ላይ አዲስና ሰፋ ያለ የጥቃት ዘመቻ ጀምሯል።
በደቡቡ የአገራችን ክልል በጉራፈርዳ የጀመረዉን አማራውን ነጥሎ የማጥቃትና የማንገላታት ዘመቻ አሁን ደግሞ በሰሜን ምስራቅ የአገራችን ክፍል በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቀጥሏል። ሰሞኑን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ለረጂም አመታት ከአካባቢዉ ህብረተሰብ ጋር ተቀላቅለው ይኖሩ የነበሩ አያሌ የአማራ ተወላጆች ያፈሩትን ንብረት ለመሰብሰብ እንኳን ግዜ ሳይሰጣቸዉ የኔ ብለው ከሚጠሩት የመኖሪያ ቦታቸዉ እንደባዳ እየተገፉ እንዲወጡ ተደርገዋል። እዚህ ላይ አንድ እጅግ የሚያሳዝን ነገር ቢኖር በገዢዉ ፓርቲ ኢህአዴግ ዉስጥ አማራን እወክላለሁ ባዩ ብአዴን ወያኔ በአማራዉ ህዝብ ላይ የሚያደርሰውን በደል ዝም ብሎ መመልከቱ ብቻ ሳይሆን ባለፈው አመት ከጉራ ፈርዳ ዘንድሮ ደግሞ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ እየተባረሩ እየወጡ ባሉ አማራዎች ላይ እየተፈጸመ ባለው ወንጀል ላይ ተባባሪ መሆኑን አሳይቷል።
ግንቦት ሰባት የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ወያኔ በአማራዉ ህዝብ ላይ ያደረሰውንና በማድረስ ላይ ያለውን ይህ ነዉ የማይባል ግፍና መከራ ከዚህ ቀደም እንዳደረገዉ ሁሉ አሁንም አጥብቆ ያወግዛል። ከዚህ በተጨማሪ ወያኔ በዚህ በኢትዮጵያ አንድነትና ነጻነት የትግል ምእራፍ ውስጥ በደም የተቀባ፣ የቀለመ አኩሪ ታሪክ ያለውን የአማራውን ህዝብ መልሶ መላልሶ የሚያጠቃውና ይህንን ታላቅ ህዝብ ከየቦታዉ የሚያፈናቅለው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን ከአማራዉ ህዝብ ጋር ብቻ በማያያዝ አገራችንን ለማዳከምና አንዱ ኢትዮጵያዊ በሌላዉ ኢትዮጵያዊ ላይ የሚደርሰዉን ግፍና መከራ “ምን አገባኝ” ብሎ እንዲመለከት ለማድረግ ባለው እጅግ አደገኛ ዕቅድ መሠረት መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲገነዘብ በጥብቅ ያሳስባል።
ከዚህም በተጨማሪ በአማራው ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ባለው እጅግ አስከፊ ወንጀል በግልም ሆነ በቡድን፣ የንጹሀንን ደም እያፈሰሳችሁ ያላችሁ ወንጀለኞችና ተባባሪዎች፣ ከያላችሁበት ታድናችሁ ለፍርድ እንድትቀርቡ ንቅናቂያችን የሚቻለውን ሁሉ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት በግልጽ እንድታውቁት ይገባል። በአማራው የደረሰው ጥቃት የሁሉም ኢትዮጵያውያን ዜጎች ጥቃት ነው እንላለን። ግንቦት ሰባት ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በግለሰብ ደረጃ የምንደሰትበትን ነጻነት የምናስጠብቀው በህብረት ነውና ወያኔ በአሁኑ ግዜ በአማራው ወገናችን ላይ የሚያደርሰውን ግፍ፤ መከራና መፈናቀል በእያንዳንዳችን ላይ እንደደረሰ በመቁጠር ይህንን ግፍ በመፈጸም የማይሰለቸውን ዘረኛ አገዛዝ በተባበረ ህዝባዊ ትግል ከአገራችን ለማስወገድ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የጋራ ትግል ጥሪ ያስተላልፋል።
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣
መጋቢት 2005 ዓ. ም

Tuesday 9 April 2013

WHAT WILL BE THE FUTURE OF ETHIOPIA?

what will be the Future of Ethiopia?
 Injustice and non democratic practice is getting worse and worse in Ethiopia since TPLF is taking over the position of governance in Home land .With a mask cover of Ethnic federalism  TPLF is distroying the people unity -working together, thinking mutual for the interest of one country, the love of one country as patriot, Ethnicity- this days in Ethiopia become a poison which killes slowely part by part, one Nation feels as differ enemys waching each other as an outcomer, because of Tplf systematic attack we become to the target circle of Tplf's plan.

People are getting arrested without accountablity of Law, any one who is against the idea of TPLF  or who have a diffrent openion will be harmed the way which is available, Their is no a free media freedom neither Journalist free practice in reporting News. so many journalists and reporters are getting arrested by proclaiming a terror-related charges, It is so sad here and then in Ethiopia to hear everything and every idea  which against the government practice is a Terrorist action, a free media is a terriorist media, an opposition party and member, and support is Terror related action. A list and last in One country to move forward in any ways is Media, if their is no communication between a giver and a receiver , a demand and supplier, and then where is an existance?
Everything is  in a silence mood, all doors are shuting down, where can the people raise their voice to be heard? The Legislative  body is Executive  and Judicial body also , same all same no partition .

Election is like free trial  dessert but not the whole menu, you can get a card   but can not choose or will not get what you belive will work.  Yes their is entitlement "Democratic" but is dangerous to practice it, Yes their is a Law but not Implementation, their is a government which is self governance! 
what elese? economy? 11% growth (Developement) ? Offcourse - Injustice, prisoned, non democracy practice, Human right violaton, corruption- a treasure of a country is owend by the TPLF memebers  they are all over it, the fund that comes fromUN and other Eu countrys is abused by TPLF memebers, while TPLF  is owning so many diffrent companies ,manufactures,Houses ,money,and so on.. yet the people of Ethiopia is luck of food ,basic need, and freedom!
 
A Brain Drain is increasing ever and people who have the opportunity to go out in any way they can are flowing out from Ethiopia because  bankruptcy of governance in Ethiopia. So many women's and men's are tormenting in Arab state Gulf region, they are victum of influence.  Regional zone becomes refugee camp that deports its own people !
  .....How many should  We  say? How long will it be like this?
Where is our National Anthem?  and what is a country without people? what will the next generation will take over? what will be the Future Ethiopia?!
Can you tell....?

Eden Abera

ESAT Daily News - Amsterdam April 06 2013 Ethiopia-ethnic cleansing

The recent forceful eviction of members of the Amhara from Benishangul-Gumuz area was an obvious case of ethnic cleansing which is a serious crime for which Rwandan officials were sentenced to life in prison.

Sunday 7 April 2013

Public Meeting in Washington DC with MP Girma Seifu (UDJ)



Girma Seifu (MP)
Awramba Times (Washington DC) – The lone opposition Member of Parliament (MP) and Vice chairman of the Unity for Democracy and Justice (UDJ), Girma Seifu will discuss with Ethiopians of all backgrounds who reside in Washington DC and surrounding areas.
According to UDJ support group in USA, the objective of the meeting is to help Finote netsanet, the official organ of UDJ on the possibility of having its own printing press to fully participate in the process of establishing democracy in Ethiopia
Date and Time: 14th April, 2013 (3:00 PM)
Place: 7701 16th St. NW Washington DC 20012