Thursday 13 December 2012

ESAT Daliy News-Amsterdam Dec. 13 2012 Ethiopia

This how Ethiopia economy is grown by far :)
while their is no Accountability and responsible government.
The mony that can be applay and can be used  for the benefit of the country has been owned by persons who is in the authority.



Monday 3 December 2012

ESAT Daliy News-Amsterdam Dec. 03 2012 Ethiopia


መድረክ በቅርቡ የተደረገውን የ3ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ሹመት ህገመንግስቱን የጣሰ ነው ሲል አወገዘ
ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ፌደራሊስት አንድነት መድረክ በቅርቡ የተደረገውን  የ3ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ሹመት ህገመንግስቱን የጣሰ ነው ሲል አወገዘ።
መድረክ ቅዳሜ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮቹ ሹመት የህገመንግስቱን ሁለት አንቀጸች የጣሰ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከምርጫ ቦርድ ጋር ውዝግብ ውስጥ የገቡ 34ቱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ህገመንግስቱ ተጥሶ 3 ም ክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች መሾማቸውን በማውገዝ ጉዳዩን ወደ ፍርድቤት ለመውሰድ የህግ ባለሙያዎችን እያማከሩ መሆኑን ገለጸዋል።

Today it is hard to be a jornalist in Ethiopia coze it will cost a freedom,things like this getting worse and worse! For Ethiopian Governement being a jornalist and exposig the fact that exist is equally seen as an oposition party for the govnt or a triorist for a country! what a shame for the govnt that call it self a democratic party!!!!!

Sunday 2 December 2012

Ethiopian refuges victum (ስደት እስከ መቼ)

ኢሳት ዜና:-የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ጉባኤውን ሲያጠናቅቅ የ77 ዳኞችን ሹመት አጽድቋል።የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው የተሾሙት አቶ ፍቅሩ አያና ከምክር ቤት አባላቱ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ቢቀርብባቸውም፣ ከፍተኛ አመራሮች ስለፈለጉዋቸው ብቻ እንዲሾሙ መደረጉን የኦህዴድ ምንጮች ገልጸዋል።


ከፍተኛ ሙስና ፈጽመዋል የተባሉት ግለሰብ የኦሮምያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ


ኢሳት ዜና:-የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ጉባኤውን ሲያጠናቅቅ የ77 ዳኞችን ሹመት አጽድቋል።የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው የተሾሙት አቶ ፍቅሩ አያና ከምክር ቤት አባላቱ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ቢቀርብባቸውም፣ ከፍተኛ አመራሮች ስለፈለጉዋቸው ብቻ እንዲሾሙ መደረጉን የኦህዴድ ምንጮች ገልጸዋል።
የምክር ቤት አባላት በአቶ ፍቅሩ ላይ ካቀረቡዋቸው የመቃወሚያ ሀሳቦች መካከል ግለሰቡ በሙስና የተዘፈቁ ናቸው፣ በዞናቸው ዳኛ ሆነው በሰሩበት ወቅት በህዝብ የተጠሉና ህዝብን ያንገላቱ ናቸው፣ የስነምግባር ችግር አለባቸው፣ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት የላቸውም የሚሉት ይገኙበታል። የክልሉ ባለስልጣናት ከምክር ቤት አባላት ለቀረበባቸው ተቃውሞ አጣርተን መልስ እንሰጣለን የሚል ድፍንፍን ያለመልስ በመስጠት ሹመቱ እንዲጸድቅ አድርገዋል።
የምክር ቤት አባላቱ በባለስልጣኑ አሰራር ላይ ነቀፌታ ሲያቀርቡ እንደነበር ታውቋል።
በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ ክልሉን ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳን ጨምሮ የስራ አስፈጻሚዎች የስልጣን ሹም ሽር ይኖራል የሚል አጀንዳ ተይዞ የነበረ ቢሆንም ምክንያቱ በውል ባልታወቀ ሁኔታ አጀንዳው እንዲሰረዝ ተድርጓል። መረጃዎች እንደሚያመለክቱት አቶ አለማየሁን ለመተካት ሀሳብ ቢቀርብም በሚተካው ሰው ላይ የስራ አስፈጻሚዎች ለመስማማት ባለመቻላቸው እንዲቀር ተድርጓል። አንዳንድ የስራ አስፈጻሚ  አባላት ስብሰባ ረግጠው እስከመውጣት መድረሳቸውን ለማወቅተ ችሎአል።
በሰሞኑ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ አርብ እለት ከተገኙት ከምክትል ፕሬዚዳንቱ ከአቶ አብዱላዚዝ በስተቀር ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት በማጠቃለያው ጉባኤ ላይ አልተገኙም።
ሰሞኑን ለአቶ ሙክታር ከድር የተሰጠው የምክትል ጠቅላይ ሚኒሰትርነት ቦታ በተወሰነ መጠን በምክር ቤቱ ውስጥ ይነሳል ተብሎ የተጠበቀውን ተቃውሞ ማብረዱ ታውቋል።
በሌላ ዜና ደግሞ አዳማ 5ኛውን ከንቲባ ሾማለች። ከሙስና ጋር በተያያዘ ከህዝብ በቀረበ ተቃውሞ ከስልጣን እንዲባረሩ በተደረጉት የተወካዮች ምክር ቤት አባሉ በአቶ ጉታ ላንጮሬ በአቶ ባካር ሻሌ ተተክተዋል። አቶ ባካር ሻሌ አቶ በረከት የሚመሩት የኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ምክት ሃላፊ የነበሩ ናቸው።
አንዳንድ ወገኖች ግለሰቡ በእርግጥም ከሙስናና ከአስተዳደር ብቃት ጋር በተያያዘ በከተማው ህዝብ ዘንድ ተቃውሞ ተነስቶባቸው የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ከስልጣናን የተባረሩት ግን ምናልባትም በኦህዴድ ውስጥ ከተፈጠረውን ችግር ጋር ተያይዞ ሊሆን እንደሚችል ይናገራሉ።
ኢሳት የከንቲባውንና የከተማ ልማት ቢሮ ሀላፊውን ከስልጣን መባረር መዘገቡ ይታወሳል።